የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ሰራተኞች እና ማኔጅመንት የዘንድሮውን የአለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፤ በህብረት እንታገል፡፡” በሚል መሪ ቃል ከክልሉ ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር በፖናል ዉይይት አክብሯል።
Category: news
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ማኔጅመንት፣ የውስጥ ኦዲተሮች እና የዋና መ/ቤት ከፍተኛ ኦፊሰሮች በተቋሙ በብዙሃኑ ቅርንጫፎች እየተተገበረ የሚገኘውን የኮር-ባንኪንግ ቴክኖሎጂ
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ማኔጅመንት፣ የውስጥ ኦዲተሮች እና የዋና መ/ቤት ከፍተኛ ኦፊሰሮች በተቋሙ በብዙሃኑ ቅርንጫፎች እየተተገበረ የሚገኘውን የኮር-ባንኪንግ ቴክኖሎጂ በሁሉም ቅርንጫፎቹ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስልጠና በመውሰድ ላይ ናቸው። ይህ ቴክኖሎጂ በሁሉም ቅርንጫፎች ተግባራዊ ሲደረግ በተቋሙ የወረቀት ስራዎችን(manual) በማስቀረት የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችንም እርካታ የሚያሳድግ ሲስተም ነው ተብሎ ይጠበቃል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከአሶሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በክልሉ የብድር አመላለስ ሁኔታን
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከአሶሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በክልሉ የብድር አመላለስ ሁኔታን አስመልክቶ ያደረገውን የጥናት ውጤት ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል።
በመድረኩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስራት ብዙአየሁ ተቋሙ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን የቁጠባ ባህል በማሻሻል የክልሉን የመልማት አቅም በማሳደግ ረገድ የተሰጠውን ተልዕኮ እየተወጣ ስለመሆኑ አመላክተዋል።
ተቋሙ የአሰራርና የተደራሽነት አድማሱን በማዘመንና በማስፋፋት በ23 ቅርንጫፎቹ እየሰጠ ባለው አገልግሎት አጠቃላይ ሀብቱን ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ማድረሱን ጠቅሰው ህብረተሰቡም በተቋሙ በመቆጠብና በመገልገል ተጠቃሚ እንዲሆን ጠይቀዋል።
የተቋሙ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አህመድ ተቋሙ ለበርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የብድር አገልግሎት በመስጠትና የቁጠባ ባህላቸውን በማሳደግ በቅርበት እያገዘ መሆኑን አስረድተዋል።
ባለድርሻ አካላትም ህብረተሰቡን በማስገንዘብና በተለያየ መንገድ የብድር አመላለስ ችግሮች እንዲፈቱ ከተቋሙ ጎን በመቆም የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አስገንዝበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎችም በጥናቱ የተቋሙን ደንበኞች የብድር አመላለስ ችግር ለመለየትና ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ለማመላከት የተሄደው እርምጃ ጥሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተቋሙን አጠቃላይ አሰራሮችና የደንበኞችን ሁኔታ ባገናዘበ ተጨማሪ ጥናቶች ተደረገው የደንበኞችን ተገልጋይነት ማሳደግና የብድር አመላለስ ስርዓቱን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።
ተቋሙ በተሻለ መንገድ ህብረተሰቡን እያገለገለ የሚገኝ አንጋፋ ተቋም እንደመሆኑ ከዚህም በተሻለ ማደግና መስፋት እንዳለበትም ተሳታፊዎቹ አንስተዋል።
በመድረኩም በቀረበው የጥናት ውጤት መነሻነት ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በቀጣይም የተቋሙን የብድር አመላለስ ችግሮች በመሰረታዊነት መቅረፍ እና የደንበኞችን ግንዛቤ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ምክረ-ሀሳቦች ቀርበውበታል።
ዘገባው የ BGM ነዉ።
በግብርናው ዘርፍ የወተት ምርት ስራ ላይ ተሰማርቶ የአሶሳን ከተማ ወተት እየመገበ የሚገኝ ታታሪ ጎልማሳ
አቶ ሲሳይ አማረ በአሶሳ ከተማ ነዋሪና የመንግስት ሰራተኛ ሲሆን በግብርናው ዘርፍ የወተት ምርት ስራ ላይ ተሰማርቶ የአሶሳን ከተማ ወተት እየመገበ የሚገኝ ታታሪ ጎልማሳ ነው፡፡
“በ2002 ዓ/ም ከሶስት ከጓደኞቼ 7 ሺ ብር ተበድሬ በአንዲት ላም በግሌ መኖሪያ ቤት ግቢ ውስጥ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡ ከውስን ዓመታት በኋላ የከብቶቹ ቁጥር ሲጨምር ስራው መስፋት የሚችል መሆኑን ስገነዘብ ከብድር እና ቁጠባ ተቋም 180 ሺ ለመጀመሪያ ጊዜ በግሌ ተበድሬ የስራው ማስፋፊያ ቦታ በመገንባት አጠናክሬ ቀጠልኩ፡፡ ስራውን እያሰፋሁ አንድም ቀን ሳልዘገይ ዕዳውንም ከፍዬ ስጨርስ ከብቶቹ በቁጥር ወደ 20 በማደጋቸው በድጋሜ 250 ሺ ብር ብድር ወስጄ ባለ-ሶስት እግር ተሸከርካሪ (የጭነት ባጃጅ) በመግዛት ስራውንም ይበልጥ አጠናከርኩ፡፡ የስራው መስፋትና እያስመዘገበ ያለው ውጤት አቅም እየሆነኝ ሲመጣ ሰፊ ቦታ ያስፈልግ ስለነበር በሁለተኛ ዙር የወሰድኩትን ብድር ዘግቼው 300 ሺ ብር ተበድሬ በአሶሳ በተለምዶ አየር መንገድ አካባቢ ሰፊ ቦታ ገዝቼ የላሞችንም ቤት ገነባሁ፡፡
በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ ስራውን ከባድ ከሚያደርጉ ሁኔታዎች መካከል መኖ ማመላለስ አንዱ ሲሆን ይህንም በጉልበቴ ከማመላለስ ጀምሮ የአህያ ጋሪ ተከራይቻለሁ….የጭነት ባጃጅ ገዝቻለሁ….አሁን ደግሞ አበዳሪ ተቋሙን አንድ ሚሊዮን ብር ብጠይቀው 800 ሺ የፈቀደልኝ ስለሆነ 3F መኪና ገዚቼ የላሞች መኖ እና የወተት ምርት ማመላለሻ አድርጌ እየተገለገልኩበት ነው፡፡ ይህ ተቋም እኔን ለስኬት ከማብቃቱም ባሻገር የክልሉ ፕሬዚዳንት ክቡር አሻድሊ ሃሰን ከካቢኔያቸው ጋር ስራ ቦታዬ ድረስ ተገኝቶ ሲጎበኙኝ በሌማት ፕሮግራም ዘርፍ የቀደመ የስኬት ተሞክሮዬን እንዳጋራቸው ምክኒያት ሆኖኛል፡፡ ይህ ስራ አሁን በጣም የሰፋ ስለሆነ ማሽን ይፈልጋል፣ የመኖ ማቀነባበሪያ ይፈልጋል፣ ዘመናዊ ማለቢያም የሚፈልግ ስለሆነ ከፍተኛ ገንዘብ የሚፈልግ ነው፡፡
እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ የገበሬ ልጅም ስለሆንኩ የእንስሳት ፍቅሩም አለኝ፡፡ ከዚህም ባሻገር በሳይንሱም ዘርፍ በመጀመሪያ ዲግሪ የእንስሳት ህክምና ባለሙያ ነኝ፡፡ በርግጥ የኑሮ ውድነቱ እየከፋ ሲመጣ የዕለት ጉርሴን ለማገዝ ብዬ ከመንግስት ስራ ጎን ለጎን ይህንን ስራ የጀመርኩት ቢሆንም ፍቅሩም ስለነበረኝ ሞያዬን ከውስጣዊ ፍላጎቴ (Passion) ጋር ለማገናኘት ነው የሞከርኩት፡፡ በመንግስት ስራ ህዝቡን እያገለገልኩ ሲሆን እዚህም በግል ስራዬ ደግሞ ከ15 በላይ ሰራተኞች አሉኝ (በስራ ዕድል ፈጠራው ዘርፍ ቀላል አይደለም)፡፡
በአሶሳ ከተማ ውስጥ በተለይም ከ6 ዓመት ወደዚህ ልጅ ያለው ሰው የላሞቼን ወተት ያውቀዋል፡፡ እኔን ጨምሮ በባለሙያ በመታገዝ ጤንነቱ የተጠበቀ፣ በጣም ጥራት ያለው ትኩስ ወተት በቀን ቢያንስ እስከ 100 ሊትር ለገበያ አቀርባለሁ፡፡ ማንም ማግኘትን ባይጠላም ገንዘብ ከማግኘት በላይ የሚያረካኝ ግን ከወተት መሸጫ ሱቆቼ በር ላይ የላሞቼን ወተት የሚጠብቁ የደንበኞቼን ፍላጎት በአግባቡ አስተናግጄ በየቤቱ ያሉት ህፃናት፣ ታማሚዎች፣ ሽማግሌዎች ትኩስ ወተት እንደደረሳቸው ሳስብ ነውና እንደ እኔ ረክቶ የሚኖር ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡
የአሁኑ ትውልድ የግብርና ስራ የሚፈራ ይመስለኛል፡፡ ግን ቆርጦ ለገባ የግብርና ስራ ውስጥ ከራስ ተርፎ ለሌሎች መብቃትም አለ፡፡ በቀጣይ እኔ ከብድር እና ቁጠባ ተቋም ጋር ሆኜ ማር እና እንቁላል ስራ እጀምራለሁ፡፡ እስካሁን ባለው መናገር የምፈልገው ከፈጣሪ ቀጥሎ የደረሰልኝ የብድር እና ቁጠባ ተቋም ባለውለታዬ ነውና ላመሰግነው እፈልጋለሁ፡፡”
ያልተጠበቀው የሸርቆሌ ቅርንጫፍ የ2014 ዓም አበራታች የስራ አፈፃፀም እና የአመራሩ ሚና!
ያልተጠበቀው የሸርቆሌ ቅርንጫፍ የ2014 ዓም አበራታች የስራ አፈፃፀም እና የአመራሩ ሚና!
“በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም የሸርቆሌ ቅርንጫፍ አሰራር ቀደም ሲል ከነበረው በአሁኑ ሰዓት “በብዙ ተሻሽሏል፡፡ በአመራር የሚደገፍ ማንኛውም ነገር ውጤታማ እንደሚሆን ስለምናምን እና ቅርንጫፉን መደገፍ ስላለብን የተቋሙን ደንብና መመሪያን ሳንነካ የህዝባችንን ተጠቃሚነትና የተቋሙንም የዕድገት ቀጣይነት ጉዳይ ማዕከል አድርገን በአሁኑ ሰዓት እንደ ወረዳው አመራር ከሰክተር አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ከቅርንጫፉ ጋር በግልፅ መድረኮች እየተነጋገርን በቅንጅት በርካታ ነገሮች አስተካክለናል፡፡ ተቋሙ መንግስታዊ እና ህዝባዊ ተቋም ነው፡፡ እኛ ደግሞ የመንግስት አካልና የህዝብ አገልጋዮች ስለሆንን እንደ አመራር ከእኛ የሚጠበቀውን እያደረግን ነው፡፡ ጥቅሙ ለትውልድ እስከሆነ ድረስ ማህበረሰባችን የማዕድን ምርት ጨምሮ ከየትኛውም ልማት ከሚያገኘው ገቢ መቆጠብ እንዳለበት የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠን አቋም ይዘን በየቀበሌው እና በተጨማሪ ህዝባዊ መድረኮች እየሰራን ነው፡፡ ከግለሰቦችን በተጨማሪ ተቋማት በተለይም እንደ ማዘጋጃ፣ ገንዘብና ኢኮኖሚ፣ የስፖርት ምክር-ቤት እና ሌሎች ገቢ ሰብሳቢ የመንግስት ተቋማት የሚያገኙትን ገቢ ሙሉ በሙሉ ከብድር እና ቁጠባ ተቋም ሸርቆሌ ቅርንጫፍ በቁጠባ እንዲያስቀምጡ ተነጋግረን ተግባራዊ እያደረግን ነው፡፡ መንግስት ያደራጃቸው የተለያዩ ማህበራትም ቢሆኑ ሃብት ሲያገኙ ድምር ውጤቱ የህዝብ እና የሃገር እድገት መሆን ስለሚገባው የሚያገኙትን ገንዘብ ከአልባሌ ጥፋት ለመታደግ በአቅራቢያቸው ያለውን የብድር እና ቁጠባ ተቋም ቅርንጫፍን መፍትሄ ማድረግ አለባቸው ብለን እየደገፍን ነው ውጤትም አምጥቷል፡፡ በአንድ ጀንበር ከ2 ሚሊዮን በላይ ቁጠባ ወደ ቅርንጫፉ የገባበትን ሁኔታ አስታውሳለሁ፡፡ የብድር አመላለሱንም በሚመለከት በትኩረት ክትትል ስለምናደርግ ቀደም ሲል የነበሩ የውዝፍ ብድር ችግሮች አሁን ላይ አይታዩም፡፡ የመንግስት ሰራተኞች ብድር በፔይሮል ተቀንሶ በወቅቱ ገቢ እየተደረገ ስለመሆኑ ስለምንከታተል ውዝፍ ውስጥ አይገባም፡፡ ትንሽ የሚያስቸግር የነበረው በየቀበሌው ያለው የገጠር ብድር ቢሆንም እሱንም ቢሆን እንደማኒኛውም የመንግስት ስራ አጀንዳ አድርገን በስምሪት ብድር እንዲመልሱ ግንዛቤ እየፈጠርን አፈፃፀሙንንም የምንከታተለው ስለሆነ እየታረመ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር ከዚህ በኋላ የሚሰራጩ ብድሮች ውዝፍ ውስጥ እንዳይገቡ ማንኛውም ደንበኛ ብድር ፈልጎ ወደ ቅርንጫፉ ሲመጣ የደንበኛውን ሁኔታ የማጥናት፣ ከዚህ በፊት ያለውን የደንበኝነቱን ሁኔታና ለስራ ያለውን ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት ጭምር የማጥናት ስራም ከቅርንጫፉ ጋር እየሰራን ነው፡፡ ምክኒያቱም ብድር የሚሰራጭበት ዋናው ምክኒያት ሰው ሰርቶ ተለውጦበት እንዲመልስ ነው እንጂ እርዳታም አለመሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በተረፈ እኛ ከምናስተዳድርበት ወረዳ ስር ያለው የብድር እና ቁጠባ ተቋም የሸርቆሌ ቅርንጫፍ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተለውጦ በክልሉ ካሉት 23 ቅርንጫፎች በተለይም በቁጠባ አሰባሰብ፣ በብድር ስርጭትና አመላለስ እንዲሁም በትርፋማነት ተሸሎ አንደኛ በመውጣት የዓመቱ ተሸላሚ መሆኑን ስንሰማ በጣም ደስ ብሎናል፡፡ ምክኒያቱም አምነንበት ነበር ከልብ የደገፍነው ውጤትም አምጥቷል፡፡ በቀጣይም ድጋፋችንን አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡” አቶ ኡመር መሃመድ(የሸርቆሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ)



(በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም የባምባሲ ቅርንጫፍ ደንበኛ)
“የብድርና ቁጠባ ተቋም ወረቴ ነው፣ በሰው ሃገር ሂዶ ከመቀጥቀጥ ተግቶ ከሰሩ ሃገራችንም ዱባይ ናት” ወ/ሮ ሉባባ ኢብራሂም ሰይድ (በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም የባምባሲ ቅርንጫፍ ደንበኛ)
በደርግ ዘመን የ7ኛ ክፍል ተማሪ የነበሩ፣ የልጆች እናት የሆኑ፣ በምግብ አብሳይነት የሰው ቤት ተቀጣሪ የነበሩ፣ የባልትና ሙያ ያላቸው፣ ልጆች ለማሳደግ 8 ዓመት በረሃ የተንከራተቱ፣ መኪና የመግዛት ህልም ስላላቸው ወደ አረብ ሃገር ሊሄዱ ሂደት ጀምረው በደላላ ቤት ሲንከራተቱ የነበሩ፣ ከ20 ሺ ብር ጀምሮ በተከታታይ ዙሮች እስከ 500 ሺ ብር ብድር በመውሰድ የባምባሲ ቅርንጫፍ የግል ብድር ደንበኛ የነበሩ፣ በባምባሲ ወረዳ መለስተኛ የሆቴል ስራ (በተለይ ምግብ) ላይ የተሰማሩ ታታሪ ሰራተኛ የሆኑ፣ በወር ከፍተኛ ገንዘብ መቆጠብ የቻሉ፣ በ1.3 ሚሊዮን ብር የህዝብ ማመላለሻ አባዱላ የገዙ፣ በ50 ዓመታቸው ማህበራዊ ሚዲያን ጨምሮ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ የሆኑ ብርቱ እማወራ ናቸው፡፡
ወ/ሮ ሉባባ ኢብራሂም ሰይድ ሲናገሩ በ1.3 ሚሊዮን የገዙት መኪና በአሁ ሰዓት ከ2.7 ሚሊዮን ብር በላይ አቅም አለው፡፡ “አባዱላ መኪናዬ ሰባት ወር እንደሰራልኝ 2 ሚሊዮን 7 መቶ ሺ ብር እንድሸጥ ተጠይቄያለሁ፡፡ ግን አልሸጥም ጊዜው አሁን ስላልሆነ፡፡ መሸጥም ካለበት በቅድሚያ መኪናው ሌላ መኪና መውለድ አለበት፡፡ ትልቁ ነገር ደግሞ ይህን 2 ሚሊዮን 7 መቶ ሺ ብር ብድርና ቁጠባ እንደሰጠኝ ነው የምቆጥረው፡፡ ተቋሙ ባያስጀምረኝ ይህ ብር ለእኔ ህልም ነበር፡፡ ወላሂ ይህ ተቋም ወረቴ ነው፡፡ አሳድጎኛል፡፡ ብር ለመበደር ሲያስቡ መጀመሪያ ሰርቶ መቆጠብን የተማርኩት ከእነሱ ነው፡፡ እኔም ህይወቴ እስካለ ድረስ ሰርቼ እንዲያልፍልኝ ነው የምፈልገው፡፡ ከተቋሙ ባለመራቄ እጅግ ተጠቅሜለሁ፡፡ ዘወትር እየሄድኩ ምክር እቀበላለሁ፡፡ ትንሽም ይሁን ትልቅ በየጊዜው እቆጥባለሁ፡፡ ዕዳ የምከፍለውም አንድ ቀን እንኳን ሳላዘገይ ነው፡፡ እኔ በአጋጣሚ በማልኖርበት ጊዜ የብድር መክፈያን ቀን ወር በገባ በ16ኛው ቀን መሆኑን ልጆቼ ያውቁታል፡፡ ይከፍላሉ፡፡
ለብድርና ቁጠባ ተቋም እና ሰራተኞቹ የማመስገኛ ቃላት የለኝም፡፡ እኔ የተሻለ የምለውን ኑሮ እየኖርኩ ከሃብታሞቹ ጋር ዕቁብ እየጣልኩ ነው። ልጆቼ ሲመጡ “የእማ ቤትኮ አረብ ሃገር ነው” ይሉኛል።ስራ ይበዛል ማለታቸው ነው። ብዙ ዕቅድ አለኝ ገና ብዙ ሰሪቼ ፈርሃ ሆኜ መኖር እፈልጋለሁ፡፡”
በ2022/23 እ.አ.አ 414.49 በላይ ቁጠባ በማሰብሰብ ከ 516.3 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በማሰራጨት በብሄራዊ ባንኩ ስታንዳርድ መሰረት ብድር ለማስመለስ እንደሚሰራ
በ2022/23 እ.አ.አ 414.49 በላይ ቁጠባ በማሰብሰብ ከ 516.3 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በማሰራጨት በብሄራዊ ባንኩ ስታንዳርድ መሰረት ብድር ለማስመለስ እንደሚሰራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም የአሶሳ ዲስትሪክት አስታወቀ፡፡
የአሶሳ ዲስትሪክት በአሶሳ ከተማ እና የመተከል ዲስትሪክት በግልገል-በለስ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን የ2021/22 እ.አ.አ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እና የ2022/23 እ.አ.አ የዕቅድ ማናበብ መድረክ ተጠናቋል፡፡
25-12-2014 ዓ.ም
አሶሳ
የብድር ጥራትን ለማስጠበቅ በደንበኛ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ እና ከአካባቢው የሥራ ባህል ጋር የሚዛመዱ እና ለተቋሙም ሆነ ለደንበኛው ውጤት ማምጣት የሚችሉ አዳዲስ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎቶችን በመቅረጽ በ2022/23 እ.አ.አ 414.49 በላይ ቁጠባ በማሰብሰብ ከ516.3 ሚሊዮን በላይ ብድር በማሰራጨት በብሄራዊ ባንኩ ስታንዳርድ መሰረት ብድር ለማስመለስ እንደሚሰራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም የአሶሳ ዲስትሪክት አስታወቀ፡፡ ዲስትሪክቱ በ2022/23 እ.አ.አ 112.99 ሚሊዮን አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስራት ብዙአየሁ እንደተናገሩት የማስፈፀም አቅም ግንባታ፣ የደንበኞች ውጤታማነትን ከምልመላ ጀምሮ በመከታተል፣ ብድርን በቁጠባ ለመሸፈን የሚያስችል ሰፊ ስልት በመንደፍ የብድር ስርጭትን በማስፋት፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ቅንጅት በማጠናከር፣ ለእስላሚክ ፋይናንሲንግ አገልግሎት እና ለኮር-ባንኪንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት በመስጠት በዲስትሪክቱ በዘርፉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አመላክቷል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ም/ ዋና/ ስራ አስፈጻሚ አቶ አድጎ አምሳያ እንደተናገሩት የዲስትሪክቱ ቅርንጫፎች ከፍተኛ የአምራችነት አቅም ያላቸው በተለይም በማዕድን ምርት፣ እርሻ፣ እርባታና ማድለብ፣ የንግድ ሥራ፣ የእንጨት ሥራ፣ ብረታ ብረት ሥራ፣ ምግብ ዝግጅት፣ ኮንስትራክሽን ላይ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በጥንቃቄ በመለየትና ከፍተኛ የፍላጎት ቁጠባ በማሰባሰብ ጥራት እና ተደራሽነት ያለው የብድር ስርጭትን ማስፋት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም በሶስቱም ዲስትሪክቶቹ በመታገዝ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎቶችን በማቅረብና የደንበኞችን ዘላቂ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በአጠቃላይ 213.92 ሚሊዮን ብር ገቢ ያገኛ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ተቋሙ አሁን ያለውን 624.9 ሚሊዮን አጠቃላይ ሃብት ወደ አንድ ቢሊዮን ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል፡፡
በተቋሙ በ2021/22 እ.አ.አ በሁሉም ዲስትሪክቶች በቁጠባ አሰባሰብ፣ ብድር ስርጭት፣ ብድር አመላለስ፣ የውዝፍ ብድር አስተዳደር መሰረታዊ መስፈርቶች የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ የሸርቆሌ፣ የዳንጉር፣ የኡንዱሉ እና አሶሳ ቅርንጫፎችን በመለየት ዕውቀናና ተጨማሪ የገንዘብ ማበረታቻዎችንም ያበረከተ ሲሆን የአሶሳ ዲስትሪክት ቅርንጫፍ ሰራተኞች የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አስፈጻሚ አካላት የዋና መ/ቤቱን የህንፃ ግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል፡፡




