(በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም የባምባሲ ቅርንጫፍ ደንበኛ)

“የብድርና ቁጠባ ተቋም ወረቴ ነው፣ በሰው ሃገር ሂዶ ከመቀጥቀጥ ተግቶ ከሰሩ ሃገራችንም ዱባይ ናት” ወ/ሮ ሉባባ ኢብራሂም ሰይድ (በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም የባምባሲ ቅርንጫፍ ደንበኛ)

በደርግ ዘመን የ7ኛ ክፍል ተማሪ የነበሩ፣ የልጆች እናት የሆኑ፣ በምግብ አብሳይነት የሰው ቤት ተቀጣሪ የነበሩ፣ የባልትና ሙያ ያላቸው፣ ልጆች ለማሳደግ 8 ዓመት በረሃ የተንከራተቱ፣ መኪና የመግዛት ህልም ስላላቸው ወደ አረብ ሃገር ሊሄዱ ሂደት ጀምረው በደላላ ቤት ሲንከራተቱ የነበሩ፣ ከ20 ሺ ብር ጀምሮ በተከታታይ ዙሮች እስከ 500 ሺ ብር ብድር በመውሰድ የባምባሲ ቅርንጫፍ የግል ብድር ደንበኛ የነበሩ፣ በባምባሲ ወረዳ መለስተኛ የሆቴል ስራ (በተለይ ምግብ) ላይ የተሰማሩ ታታሪ ሰራተኛ የሆኑ፣ በወር ከፍተኛ ገንዘብ መቆጠብ የቻሉ፣ በ1.3 ሚሊዮን ብር የህዝብ ማመላለሻ አባዱላ የገዙ፣ በ50 ዓመታቸው ማህበራዊ ሚዲያን ጨምሮ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ የሆኑ ብርቱ እማወራ ናቸው፡፡

ወ/ሮ ሉባባ ኢብራሂም ሰይድ ሲናገሩ በ1.3 ሚሊዮን የገዙት መኪና በአሁ ሰዓት ከ2.7 ሚሊዮን ብር በላይ አቅም አለው፡፡ “አባዱላ መኪናዬ ሰባት ወር እንደሰራልኝ 2 ሚሊዮን 7 መቶ ሺ ብር እንድሸጥ ተጠይቄያለሁ፡፡ ግን አልሸጥም ጊዜው አሁን ስላልሆነ፡፡ መሸጥም ካለበት በቅድሚያ መኪናው ሌላ መኪና መውለድ አለበት፡፡ ትልቁ ነገር ደግሞ ይህን 2 ሚሊዮን 7 መቶ ሺ ብር ብድርና ቁጠባ እንደሰጠኝ ነው የምቆጥረው፡፡ ተቋሙ ባያስጀምረኝ ይህ ብር ለእኔ ህልም ነበር፡፡ ወላሂ ይህ ተቋም ወረቴ ነው፡፡ አሳድጎኛል፡፡ ብር ለመበደር ሲያስቡ መጀመሪያ ሰርቶ መቆጠብን የተማርኩት ከእነሱ ነው፡፡ እኔም ህይወቴ እስካለ ድረስ ሰርቼ እንዲያልፍልኝ ነው የምፈልገው፡፡ ከተቋሙ ባለመራቄ እጅግ ተጠቅሜለሁ፡፡ ዘወትር እየሄድኩ ምክር እቀበላለሁ፡፡ ትንሽም ይሁን ትልቅ በየጊዜው እቆጥባለሁ፡፡ ዕዳ የምከፍለውም አንድ ቀን እንኳን ሳላዘገይ ነው፡፡ እኔ በአጋጣሚ በማልኖርበት ጊዜ የብድር መክፈያን ቀን ወር በገባ በ16ኛው ቀን መሆኑን ልጆቼ ያውቁታል፡፡ ይከፍላሉ፡፡

ለብድርና ቁጠባ ተቋም እና ሰራተኞቹ የማመስገኛ ቃላት የለኝም፡፡ እኔ የተሻለ የምለውን ኑሮ እየኖርኩ ከሃብታሞቹ ጋር ዕቁብ እየጣልኩ ነው። ልጆቼ ሲመጡ “የእማ ቤትኮ አረብ ሃገር ነው” ይሉኛል።ስራ ይበዛል ማለታቸው ነው። ብዙ ዕቅድ አለኝ ገና ብዙ ሰሪቼ ፈርሃ ሆኜ መኖር እፈልጋለሁ፡፡”

“ከ500 ብር ጀምሮ በዕቁብ መልክ በቡድን በቆጠብነው 50 ሺ ብር ዋስትና ተነስተን ዛሬ ባለ-ሃብት እየተባልን ነው፡፡ አልሃምዱሊላህ ከዚህ በላይ እናድጋለን፡

“ከ500 ብር ጀምሮ በዕቁብ መልክ በቡድን በቆጠብነው 50 ሺ ብር ዋስትና ተነስተን ዛሬ ባለ-ሃብት እየተባልን ነው፡፡ አልሃምዱሊላህ ከዚህ በላይ እናድጋለን፡፡ ህብረተሰቡ ሲጠቀም እንደወጣት እኛም እናድጋለን፡፡” አቶ ሁሴን አልሂሰን (በኡራ ወረዳ የባሻቡዳ ቀበሌ ነዋሪ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ ተቋም የአሶሳ ቅርንጫፍ ደንበኛ)

ቀደም ሲል በሹፍርና ሙያ ይተዳደር የነበረ፣ 50 ሺ ብር ቆጥቦ ከ250 ሺ ብር ጀምሮ የአሶሳ ቅርንጫፍ የቡድን ብድር ደንበኛ የሆኑ፣ በወሰዱት ብድር ስርተው የእርሻ ትራክተር እና የእህል ወፍጮ ባለቤት የሆኑ፣ በአሁኑ ሰዓት በቀን ከ18 በላይ ሰራተኛ የሚያሰራ 5 ዓባላት ያሉት አልሂሰን፣ መሪየምና ጓደኞቹ የሚባል የእርሻ ስራ ማህበር ያደራጁ ናቸው።

“የስኬታችን ሚስጥር ፅናትና ብርታት ነው፡፡ ብድሩን ለጫት፣ ለሲጋራ፣ ለጠላ ቤት አላዋልነም፡፡ የስራ እንጂ የሻይ ሱስ እንኳን የለብንም፡፡ ማህበራችንን አልበተንነም፣ ገንዘብ አልተከፋፈልነም፣ ወጪ እንጂ አስተማማኝ ገቢ የለለውን ሞተር ሳይክል እንኳን አልገዛንበትም፡፡ እኛ የገዛነው የግብርና ግብዓት ነው፡፡ ከዚያም በ20 ሺ ብር ትራክተር ተከራይተን 8 ሄክታር አለማን፡፡ በ8 ሄክታር ያለማነው ፍሬ ሲያፈራ ትራክተር ገዛን፡፡ የወሰድነውን ብድር ለስራ ዓላማ ነው ያዋልነው፡፡ የማህበረሰባችን ጥያቄ የነበረው የዕህል ወፍጮም ገዝተን አገልግሎት እየሰጠ ነው።

በመጀመሪያ ዙር ትራክተር ገዝተናል፡፡ በገዛነው ትራክተር በዚህ ዓመት በ17 ሄክታር ላይ ያመረትነው አኩሪአተር፣ በቆሎ፣ በርበሬ፣ ማሽላ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኝ ነው፡፡ ከበርበሬ ምርት ብቻ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ገቢ እንጠብቃለን፡፡ አልሃምዱሊላህ በደንብ ነው ያፈራልን፡፡ ማሽላ በ8 ሄክታር ላይ ዘርተናል፡፡ ከዚህም ከ400 ኩንታል በላይ እንጠብቃለን፡፡

ወጣቱ ጫት፣ ሺሻ፣ ሲጋራ መተው አለበት፣ የቀደሙት በተለይም ወላጆቻቸው የሚናገሩትን መስማት አለባቸው፡፡” ( አቶ ሁሴን አልሂሰን የማህበሩ ሊቀመንበር)

+3

All reactions:

88Guteta Birhanu, Amuna Asemani and 86 others