Skip to content
የተቋሙ ዓላማ
- በግብርናና ከግብርና ውጭ ለሚደረገው ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የብድር አገልግሎት መስጠት፣
- የደሃውን ህዝብ ካፒታል በማሳደግ እና ገቢውን በማብቃቃት የመቆጠብ ባህሉእንዲዳብር ማድረግ፣
- በግለሰቦች ዕጅ ያለስራ ተበታትኖ የሚገኘውን ገንዘብ በቁጠባ በማሰባሰብ በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ህብረተሰብ ክፍሎችንየብድር አገልግሎትበማቅረብና ተጠቃሚ በማድረግ ከድህነት ማላቀቅ፣
- የብድር አቅርቦት በመስጠት ህብረተሰቡን ከአራጣ አበዳሪዎች ብዝበዛ ነፃ ማውጣት፣
- ህብረተሰቡን በብድርና ቁጠባ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ማድረግ፣
- የድኃ ድኃ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በልዬ ትኩረት የብድርና ቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፣
- የሴቶችንና ወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ልዬ ትኩረት መስጠት፣
- ቁጠባን ከብድር ጋር አስተሳስሮ ከባህላዊው ወደ ዘመናዊ በማሸጋገር ትኩረት ሰጥቶ መስራት፣
- ለተለያዬ ቴክኖሎጅዎች ብድር በማቅረብ ምርትና ማሳደግ ናቸው፡፡