የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ማኔጅመንት፣ የውስጥ ኦዲተሮች እና የዋና መ/ቤት ከፍተኛ ኦፊሰሮች በተቋሙ በብዙሃኑ ቅርንጫፎች እየተተገበረ የሚገኘውን የኮር-ባንኪንግ ቴክኖሎጂ በሁሉም ቅርንጫፎቹ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስልጠና በመውሰድ ላይ ናቸው። ይህ ቴክኖሎጂ በሁሉም ቅርንጫፎች ተግባራዊ ሲደረግ በተቋሙ የወረቀት ስራዎችን(manual) በማስቀረት የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችንም እርካታ የሚያሳድግ ሲስተም ነው ተብሎ ይጠበቃል።