የቤንሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ አ.ማ አዲሱ የህንፃ ምርቃት የክልላችን ርዕሰ-መስተዳድር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን እና የተቋማችን የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሳ አህመድ እና አባላት በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል::

የጠቅላላጉባኤስብሰባጥሪንይመለከታል

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማኅበር በምዝገባ ቁጥር ሐ-8-81-31922 መሰረት የአክሲዎን ድርሻ በመክፈል አባል መሆናቸው ይታወቃል፡፡  

ስለሆነም የአክሲዮን ማኅበሩ ባለ-አክሲዮኖች 3ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኝበት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ በዋና መ/ቤት ህንጸ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የሚካሄድ ሲሆን የእለቱ አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው

  1. የ3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች
    1.  ምልዐተ ጉባኤው መሟላቱን ማረጋገጥና ማጽደቅ
    1.  የጉባኤውን ድምጽ ቆጣሪ መሰየም
    1.  የአክሲዮን ማኅበሩን ካፒታል ማሳድግ
    1.  የአክሲዮን ማኅበሩን የተጠራቀመ ትርፍ ወደ ተከፈለ ካፒታል ማዞር ናቸው፡፡

በመሆኑም የተከበራችሁ የባለ-አክሲዮን ተወካዮች በተጠቀሰው ቀን እና ሰአት ማንነተዎን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ጉባኤው ላይ እንዲገኙ፤እርሰዎ ካልቻሉ ህጋዊ ወኪለዎ የውክልና ደብዳቤ እና ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ እንዲቀርቡ በአክብሮት ተጠርተዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *