የጠቅላላጉባኤስብሰባጥሪንይመለከታል
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማኅበር በምዝገባ ቁጥር ሐ-8-81-31922 መሰረት የአክሲዎን ድርሻ በመክፈል አባል መሆናቸው ይታወቃል፡፡
ስለሆነም የአክሲዮን ማኅበሩ ባለ-አክሲዮኖች 3ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኝበት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ በዋና መ/ቤት ህንጸ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የሚካሄድ ሲሆን የእለቱ አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው
- የ3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች
- ምልዐተ ጉባኤው መሟላቱን ማረጋገጥና ማጽደቅ
- የጉባኤውን ድምጽ ቆጣሪ መሰየም
- የአክሲዮን ማኅበሩን ካፒታል ማሳድግ
- የአክሲዮን ማኅበሩን የተጠራቀመ ትርፍ ወደ ተከፈለ ካፒታል ማዞር ናቸው፡፡
በመሆኑም የተከበራችሁ የባለ-አክሲዮን ተወካዮች በተጠቀሰው ቀን እና ሰአት ማንነተዎን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ጉባኤው ላይ እንዲገኙ፤እርሰዎ ካልቻሉ ህጋዊ ወኪለዎ የውክልና ደብዳቤ እና ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ እንዲቀርቡ በአክብሮት ተጠርተዋል፡፡

