የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ማኔጅመንት፣ የአሶሳ ዲስትሪት እና የቅርንጫፎቹ ስራ አስኪያጆች የአመራር እና የደንበኛ አያያዝ ክህሎት ስልጠና በቢዝነስ ደቨሎፕመንት እና ሪሰርች ስራ ክፍል በመታገዝ ሰሞኑን ወስደዋል።
የተሻለ የአመራር ቁርጠኝነት በማስፈን፣ አውንታዉ የአመለካከት ለውጥ በማምጣት፣ የዳበረ የባለቤትነት ስሜት በማጎልበት፣ የተሻለና ዉጤታማ የደንበኛ አያያዝ በማስፈን የላቀ የጋራ ዉጤት ከማስመዝገብ አኳያ እምርታዊ ለውጥ ለማምጣት ስልጠናው የሚያግዝ ነው ተብሎ ይጠበቃል።